የከተሜነት መስፋፋት የማይቀር ጉዳይ ነው !

You are currently viewing የከተሜነት መስፋፋት የማይቀር ጉዳይ ነው !
  • Post category:ልማት

👉 በ 2050 አብዛኛው አፍሪካዊ ፣ አብዛኛው የዓለም ህዝብ ከተሜ ይሆናል፤ ከተሜነት ይስፋፋል። ይህ አይቀሬ ጉዳይ ነው። በኢትዮጵያ በከተሜነት ግንባታ በኮሪደር ልማት እየመጣ ያለው ለውጥ የማይታየው አንድ ዜጋ ካለ ያሳዝናል።

👉 አዲስ አበባ ብቻ አይደለም በመላ ሀገሪቱ እንቅስቃሴው አለ። ከቢሮ ፣ ከግቢ በመጀመር አዲስ አበባ ላይ ከዛም ወደ ሁሉም አካባቢዎች እናሰፋለን ባልነው መሰረት ፣ በገባነው ቃል መሰረት ከቢሮ የጀመርነው ስራ አሁን ላይ ብዙ ከተሞችን አዳርሷል።

👉 በየከተማው በዕቅድ የሚመራ የሚኖርበት እና የሚሰራበት አካባቢ ካልፈጠርን ሁሉም ወደ አንድ ከተማ ካልመጣ ሲጀመርም በቂ ፕላን እና መሰረተ ልማት ስላልነበረ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ችግሩን ያባብሰዋል።

👉 ትልቅ ህዝብ ያለው ሀገር ስለሆነ በርከት ያሉ ከተሞችን በመፍጠር ፣ ከተሜነት እየተፈጠረ ሲሄድ በከተማ ውስጥ ጤናማ ህይወት መኖር የሚችሉ ፣ አካባቢያቸውን የሚወዱ፣ በሰላም ወጥተው የሚገቡ ፣ በቂ አገልግሎት የሚያገኙ ዜጐች ይበራከታሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በ6ኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 10ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ በም/ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ከሰጡት ማብራሪያ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review