AMN- ጥር 28/2018 ዓ.ም
ባለፉት 5 ዓመታት በተከናወኑ ተግባራት የወጣቱን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ እና ፖለቲካዊ ተሳትፎ ያሳደጉ ስራዎች እውን ማድረግ ተችሏል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን ተናገሩ ::
ቢሮው ከሲቪክ ማህበራት አደረጃጀቶች ጋር ባለፉት አምስት ዓመታት በተሰሩ ስራዎች ዙሪያ ውይይት አድርጓል፡፡:
የቢሮው ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን፣ ባለፉት አምስት ዓመታት የወጣቱን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተሰርተዋም ብለዋል።
በዚህም ተግባርም 1.6 ሚሊየን ለሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል ተፈጥሯልም ሲሉ አክለዋል፡፡:
ሌላው ወጣቶች ባለፉት ዓመታት ፖለቲካዊ ተሳትፎቸው እንዲጎለብት በተሰራው ስራም በተለያዩ ተቋማት በአመራርነት እና በውሳኔ ሰጭነት ላይ እንዲሰማሩ መደርጉንም ኃላፊው አብራርተዋል::
7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ዲሞክራሲያዊ እና ፍትሃዊ እንዲሆን የሲቪክ ማህበራትና ወጣቶች ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አቶ በላይ አሳስበዋል::
ባለፉት 5 ዓመታት ብቻም በድግግሞሽ 4.3 ሚሊየን ወጣቶች በተለያዩ በጎ ፍቃድ ስራዎች ላይ መሳተፋቸውም በመድረኩ ተመላክቷል::
በቴዎድሮስ ይሳ