• ቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ ጥቁር አፍሪካዊት ሀገር በመሆኗ ለአፍሪካውያን “የነጻነት ቀንዲል” ሆና መታየቷ፣
• ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ የምትገኝና ለሰሜን፣ ለደቡብ፣ ለምሥራቅና ለምዕራብ አፍሪካ ሀገራት አማካይ ርቀት ላይ በመገኘቷ ለጉዞና ለግንኙነት ምቹ ሆና በመገኘቷ፥
• የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከአውሮፓና ከእስያ ጋር የሚያገናኝ ቀዳሚ አየር መንገድ በመሆኑ ዲፕሎማቶችና መሪዎች በቀላሉ ወደ አዲስ አበባ እንዲመላለሱ ትልቅ ዕድል መፍጠሩ፥
• በአጼ ኃይለ ሥላሴ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት በሁለቱ ተፋላሚ ጎራዎች (ሞንሮቪያ እና ካዛብላንካ ግሩፕ) መካከል የነበረው ልዩነት በማስታረቃቸው አዲስ አበባ በሁሉም ዘንድ ተቀባይነት ማግኘቷ፣
• ድርጅቱ ሳይመሠረት አዲስ አበባ ዘመናዊ የስብሰባ አዳራሽ (Africa Hall) እና ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችን ገንብታ መጠበቋ፣ መሪዎቹ ሌላ አማራጭ እንዳያማትሩ ማድረጉ፣
• አዲስ አበባ ከቀን ወደቀን በማያቋርጥ ዕድገት ውስጥ የምትገኝ በመሆኗ በየጊዜው የፈጠረችው ተቀባይነት የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የአፍሪካም መዲና እንድትሆን አድርጓታል።