ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ እና በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራረሙ

You are currently viewing ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ እና በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራረሙ

AMN የካቲት

ኢትዮጵያ እና አዘርባጃን በመከላከያ እና በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመግባቢያ ሰነዶችን ተፈራርመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልዕክት በአዘርባጃን ባደረግኩት የመጀመሪያ ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ፕሬዝዳንት ኢልሃም አሊዬቭ ላደረጉልኝ ሞቅ ያለ እና የተከበረ አቀባበል ልባዊ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

‎ባለፉት ጥቂት ዓመታት በአቪዬሽን ዘርፍ፣ በኢንዱስትሪ ፓርኮች እና በነፃ የንግድ ቀጣናዎች፣ እንዲሁም በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ እና በአዘርባጃን አቻው መካከል በተደረጉ የኢኮኖሚ ትብብሮች ላይ በመመስረት አጋርነታችን በየጊዜው እያደገ መጥቷል ብለዋል።

እነዚህ የትብብር ዘርፎች ለሁለትዮሽ ግንኙነታችን መጠናከር መሠረት የጣሉ ሲሆን፣ ዛሬ ባደረግነው ጥልቅ ውይይትም ግንኙነታችንን እና ትብብራችንን ይበልጥ ለማጠናከር እና ወደ ላቀ ደረጃ ለማሳደግ ተስማምተናል።

‎በዛሬው ዕለትም በመከላከያ እና በሌሎች ዘርፎች ዙሪያ የመግባቢያ ሰነዶች ፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝተናል ብለዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review