AMN – የካቲት 30/2018 ዓ.ም
የእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የሩብ ፍፃሜ ዕጣ ድልድል ከደቂቃዎች በፊት ይፋ ሆኗል።
በድልድሉ መሰረት ማንችስተር ሲቲ ከ ሊቨርፑል የሚያደርጉት ፍልሚያ ከወዲሁ ትልቅ ቦታ ተሰጥቶታል።
የፕሪምየር ሊጉ መሪ አርሰናል ወደ ሴንት ሜሪ ስታዲየም አቅንቶ ሳውዛምፕተንን ይገጥማል።
ቼልሲ የሊግ 1 ተወዳዳሪው ፖርት ቬልን በሜዳው ስታምፎርድ ብሪጅ የሚያስተናግድበት ጨዋታም ይጠበቃል።
የዌስትሃም ዩናይት እና ብሬንትፎርድ አሸናፊ ከ ሊድስ ዩናይትድ የሚያደርጉት ጨዋታ ሌላው የሩብ ፍፃሜ ግጥሚያ ነው።
በሸዋንግዛው ግርማ