ሀገራዊ ለውጡ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ መስኮች ያስገኛቸው ዋና ዋና ዉጤቶች

You are currently viewing ሀገራዊ ለውጡ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ መስኮች ያስገኛቸው ዋና ዋና ዉጤቶች

AMN መጋቢት 24/2018 ዓ.ም

ሀገራዊ ለውጡ በኢትዮጵያ ሁለንተናዊ መስኮች ያስገኛቸው ዋና ዋና ዉጤቶች

ለውጡ ከመጣ በኋላ በፖለቲካው ዘርፍ የታዩ ጉልህ ለውጦች፦

👉 የምህረት አዋጅና የፖለቲካ እስረኞች መፈታት፡ በውጭ ሀገር በስደት የነበሩ የፖለቲካ ድርጅቶችና ታጣቂዎች ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው በሰላማዊ መንገድ እንዲታገሉ ተደርጓል።

👉 የተቋማት ግንባታ፡ የምርጫ ቦርድ፣ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የፍትህ አካላት ከፖለቲካ ተጽዕኖ ነፃ ሆነው እንዲደራጁ ጥረት ተደርጓል።

👉 ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን፡ ለዘመናት የቆዩ መሠረታዊ የፖለቲካ ልዩነቶችን በውይይት ለመፍታት የሚያስችል ነፃ ኮሚሽን ተቋቁሞ ወደ ሥራ ገብቷል።

 የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች

ሀገሪቱ የነበረባትን የዕዳ ጫና ለመቀነስና የግል ዘርፉን ለማበረታታት የተከናወኑ ተግባራት፦

👉 የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ፡ በቅርቡ የተተገበረው ሙሉ የውጭ ምንዛሬ ተመን ማሻሻያ፤ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለመሳብና የጥቁር ገበያን ለማጥፋት ያለመ ነው

👉 የግል ዘርፍ ተሳትፎ፡ ቀደም ሲል በመንግሥት ብቻ ተይዘው የነበሩ ዘርፎች (ለምሳሌ የቴሌኮም ዘርፍ) ለግል ባለሀብቶች ክፍት ሆነዋል።

👉 የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ፡ “ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025” ስትራቴጂን በመቅረፅ የክፍያ ሥርዓቶችንና የመንግሥት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ የማድረግ ስራ በስፋት ተከናውኗል።

 የምግብ ዋስትናና የግብርና ምርታማነት

በግብርናው ዘርፍ የታዩ ስኬቶች

👉 የስንዴ ልማት ፦ ኢትዮጵያ ስንዴን ከውጭ ከማስገባት ባለፈ ለውጭ ገበያ ማቅረብ የጀመረችበት የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ትልቅ ስኬት ነው።

👉 የሌማት ቱሩፋት፦ በየቤተሰብ ደረጃ የዶሮ፣ የቀንድ ከብትና የንብ ማር ምርትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ የተከናወነ ንቅናቄ ነው።

 የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ

👉 ለውጡ ግድቡ ከነበረበት ሁኔታ ወጥቶ እንዲጠናቀቅና ኃይል ማመንጨት እንዲጀምር አድርጓል።

👉 ይህ ለሀገሪቱ የኢንዱስትሪ ዕድገትና ለኃይል ሽያጭ ትልቅ ሚና አለው።

 የአረንጓዴ አሻራና የቱሪዝም ልማት

👉 የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር፡ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የተከናወነው ሥራ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና አስገኝቷል።

👉 የቱሪዝም መዳረሻዎች፡ በታሪካዊና ተፈጥሯዊ ስፍራዎች (እንደ አንድነት ፓርክ፣ ወንጪ፣ ጎርጎራ እና ኮይሻ) የተገነቡ ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን የቱሪዝም ገቢ አሳድገዋል።

 የዲፕሎማሲ ስኬቶች

👉 የብሪክስ (BRICS) አባልነት፡ ኢትዮጵያ የዓለም ግዙፍ የኢኮኖሚ ስብስብ የሆነው የብሪክስ አባል መሆኗ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን ተሰሚነት ይጨምራል።

👉 የሰላም ስምምነት፡ በትግራይ ክልል የነበረውን ጦርነት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት መቻሉ ለሀገራዊ መረጋጋት ትልቅ ፋይዳ አለው።

በሚካኤል ህሩይ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review