የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ ከዓለም አቀፍ ገንዘብ ድርጅት ስብሰባ ጎን ለጎን ከሳዑዲ ዓረቢያ የልማት ፈንድ ዋና ሥራ አስኪያጁ ሱልጣን አብዱረሃማን አልማርሻድ ጋር ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ውይይቱ ኢትዮጵያ በቅርቡ በተገበረችው የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም እንዲሁም በኢትዮጵያ ቅድሚያ በሚሰጣቸው የልማት መስኮች ላይ ያተኮረ እንደነበር የሚኒስቴሩ መረጃ ያሳያል።