የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ

You are currently viewing የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፈ

AMN – ሐምሌ 27/2017 ዓ.ም

ለወዳጅነት ጨዋታ ወደ ዩናይትድ ስቴት አሜሪካ ያቀናው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዲ ሲ ዩናይትድን 3ለ0 አሸነፈ ።

ለዋልያዎቹ ከነአን ማርክነህ ፣ ዳዋ ሆቴሳ እና ረመዳን የሱፍ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል ።

ዋሺንግተን በሚገኘው ኦውዲ ፊልድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ባለሜዳው ዲ ሲ ዩናይትድ ከስድስት በላይ የአካዳሚ ተጫዋቾችን ተጠቅሟል ።

ሙሉ ወጪያቸው ተሸፍኖ ወደ አማሪካ ያቀኑት የቡሔራዊ ቡድኑ አባላት 20 ሺ ዶላር ይበረከትላቸዋል ።

ጨዋታውን በድል በመወጣታቸው ደግሞ ቃል የተገባላቸው የ50ሺ ዶላር ጉርሻ የሚሰጣቸው ይሆናል ።

በሸዋንግዛው ግርማ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review