በሚቀጥሉት ወራት ለመመረቅ ወረፋ የሚጠብቁ ግድቦች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ

You are currently viewing በሚቀጥሉት ወራት ለመመረቅ ወረፋ የሚጠብቁ ግድቦች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ
  • Post category:ልማት

‎AMN ጥቅምት 14 /2018 ዓ.ም

በሚቀጥሉት ወራት ለመመረቅ ወረፋ የሚጠብቁ ግድቦች መኖራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ

‎ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የ2018 ዓ.ም የመጀመሪያ 100 ቀናት የማክሮኢኮኖሚ አፈፃፀም ግምገማ በኮይሻ ግድብ ከሚኒስትሮች ጋር አድርገዋል።

‎በውይይቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ( ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ ኢትዮጰያ ውስጥ የመፍጠር እና መፍጠን አስፈላጊነት በግልጽ መታየት መጀመሩን ገልፀዋል።

‎በአገር አቀፍ ደረጃ በሺዎች የሚቆጠሩ ኘሮጀክቶች መኖራቸውን ገልፀው፣ እንዲሰሩ መከታተልም ከተጠናቀቁ በኃላ ማስመረቅም ስራ እየሆነ መምጣቱን አመላክተዋል።

‎በርካታ ኘሮጀክቶች የማስመረቅ ጥያቄ ቢቀርብም በኘሮግራም መጣበብ ምክንያት እንደሚቸገሩ ነው የገለፁት።

‎ለአብነት የግድብ ፕሮጀክቶችን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቅርቡ ሶማሌ ክልል የሚገኘው ግድብ፣የታላቁ ህዳሴ ግድብ፣ ወልመል፣ መመረቃቸውን እና በሚቀጥሉት ወራት ደግሞ ለመመረቅ ወረፋ የሚጠብቁ ግድቦች መኖራቸው አስረድተዋል።

‎እነዚህ ከመካከለኛ እስከ ከፍተኛ የሚባሉ ግድቦች መሆናቸውን፣ ለመስኖ እና የኤሌክትሪክ ሀይል የሚያመነጩ ያለቁ እና ምርቃት የሚጠብቁ ኘሮጀክቶች እንደሆኑ ገልፀዋል ።

‎ወደ እንደዚህ አይነቱ አውድ ያስገባን መፍጠር እና መፍጠን ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ እንፍጠን እንትጋ ከልፋታችን ውጪ የሚለወጥ ሀገር አይኖርም የሚለው እሳቤ በእጅጉ ማገዙን ነው የገለፁት።

‎በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review