‎ማየትና ማለም ትልቅ ዓቅም እና ጉልበት መሆኑን በአዲስ አበባ በተገነቡ መሰረተ ልማቶች አይተናል

You are currently viewing ‎ማየትና ማለም ትልቅ ዓቅም እና ጉልበት መሆኑን በአዲስ አበባ በተገነቡ መሰረተ ልማቶች አይተናል

AMN- ጥቅምት 30/2018 ዓ.ም

‎የማየትና የማለም አቅም ምን ያህል ጉልበት እንዳለው በከተማዋ በተሰሩ የልማት ስራዎች አይተናል ሲሉ የፍትሕ ሚንስትር ዴኤታ አቶ ኤርሚያስ የማነብርሀን ገለፁ ።

‎የብልፅግና ከፍተኛ አመራሮች በመዲናዋ የተሰሩ የልማት ስራዎችን የጎበኙ ሲሆን በጉብኝቱም የተገኙ አመራሮች በከተማ ስለተሰሩ ልማቶች አስተያየታቸውን ለኤ ኤም ኤን ሰጥተዋል።

‎የመዲናዋን የልማት ስራዎችን የጎበኙት የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኤርሚያስ የማነብርሀን በከተማዋ የተመለከቱት ውበት እንዳስደነቃቸው ገልፀዋል።

‎በአጠቃላይ ከግዜው አንፃር የማየት እና የማለም አቅም ምን ያህል ጉልበት እንዳለው በከተማዋ በተሰራው ስራ ተመልክተናል ሲሉ ተናግረዋል ።

‎በከተማዋ የተገነቡትን ዘርፈ ብዙ የልማት ሰራዎች ወደ መሬት እንዲወርዱ የወጠኑ፣ ያሰቡት እና ተግባራዊ እንዲሆኑ ሀላፊነትን የወሰዱ አመራሮችን አመስግነዋል፡፡ ይህ ስራ በስፋት ሲሰራ በሌሎች ሀገሮች የምናያቸው ነገሮች ቅንጦት አይሆኑብንም ብለዋል ።

እስከዛሬ ላለመለወጣችን የፋይናንስ እና የሃብት ችግር ሳይሆን የማየትና የእንችላለን የማለት ክፍተት እንደነበር አስታውሰዋል።

‎በሔለን ተስፋዬ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review