በየዓመቱ በህዳር ወር ላይ ቆሻሻን የማቃጠል ተግባር ከማጽዳት ይልቅ አከባቢን መበከል ነው

You are currently viewing በየዓመቱ በህዳር ወር ላይ ቆሻሻን የማቃጠል ተግባር ከማጽዳት ይልቅ አከባቢን መበከል ነው

‎AMN ህዳር 11/2018 ዓ.ም

‎በየዓመቱ በህዳር ወር ላይ ቆሻሻን የማቃጠል ተግባር እየቀነሰ ቢመጣም ችግሩ ሙሉ በሙሉ አለመወገዱን የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር አጀንሲ እና የአዲስ አበባ ከተማ የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቁ ፡፡

‎የባለስለጣኑ የአካባቢ ሕግ ተከባሪነት ዳይሬክተር አቶ ለሜሳ ጉደታ እንደተናገሩት ፣ ቆሻሻን የማቃጠል ልምምድ አካባቢን ከማጽዳት ይልቅ አከባቢን የሚበክል በመሆኑን ገልፀዋል።

‎ፕላስቲክ ቆሻሳችን ማቃጠል እንደ ካንሰር ላሉ በሽታዎች እደሚዳርግ በመገንዘብ፤ ህብረተሰቡ በራሱ እና በአከባቢው ላይ ከሚደርስ አደጋ መታደግ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

‎ቆሻሻን የማቃጠል ጉዳዩ ላይ ህብረተሰቡ የባህሪ ለውጥ በማምጣት ተግባሩን ሙሉ በሙሉ ማስቀረት ይገባልም ብለዋል፡፡

‎የአዲስ አበባ ከተማ ጽዳት አስተዳደር አጀንሲ ምክትል ስራ አስኪያጅ አቶ ሙላት ተገኘ በበኩላቸው፣ በህዳር ወር ላይ የሚደረገውን ቆሻሻን የማቃጠል ልምድ ለማስቀረት “ህዳር ሲፀዳ” በሚል ሰፊ የንቅናቄ ስራዎች እየተከናወነ ስለመሆኑም አንስተዋል፡፡

‎ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ ጎን ለጎን ተግባሩን በሚፈጸሙ አካላት ላይ እርምጃ እንደሚወሰድባቸው ጠቁመዋል፡፡

‎ በጽዮን ማሞ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review