AMN-ጥቅምት 15/2017 ዓም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከሚኒስትሮች ልዑካን ቡድን ጋር ማሌዢያ ኳላላምፑር ገብተዋል ።
በብሪክስ ጉባኤ የነበራቸውን ቆይታ ያጠናቀቁት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከሚኒስትሮች ልዑካን ቡድን ጋር በመሆን ለይፋዊ ጉብኝት ማሌዢያ ኳላላምፑር መግባታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል ።