አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጰያ ያሰበችውን ግብ ማሳካት እንደምትችል ማሳያ መሆኑን ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ

You are currently viewing አረንጓዴ አሻራ ኢትዮጰያ ያሰበችውን ግብ ማሳካት እንደምትችል ማሳያ መሆኑን ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለጹ

‎AMN- ሐምሌ 24/2017 ዓ.ም

‎የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ኢትዮጰያ ያሰበችውንና ያስቀመጠችውን ግብ ማሳካት እንደምትችል ማሳያ እንደሆነ የግብርና ሚንስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ገለፁ።

‎ባለፈው ዓመት 600 ሚሊየን ችግኞች በአንድ ጀንበር ለመትከል ታቅዶ 650 ሚሊየን ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል።

‎በዘንድሮ ዓመት 700 ሚሊየን ችግኞችን በዛሬው ዕለት እንደሚተከሉ እና የሚተከሉትም በጂኦግራፊካል ቦታቸው የተለዩና አይነቶቹም እንደየአከባቢው መለየታቸውን ገልፀዋል።

‎በእያንዳንዱ ኢትዮጰያዊ የሚተከለው ችግኞች ከግዜያዊ ማስተባበርያ በቀላሉ መከታተል እንደሚቻልም ተናግረዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review