ኢትዮጵያ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ቀንዲል መሆን የቻለችው በጀግኖች ልጆቿ ፅናትና አይበገሬነት መሆኑ ተገለፀ

You are currently viewing ኢትዮጵያ የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ቀንዲል መሆን የቻለችው በጀግኖች ልጆቿ ፅናትና አይበገሬነት መሆኑ ተገለፀ

AMN ጳጉሜን 1/2017 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ጳጉሜን 1 የፅናት ቀንን በተለያዩ መርሃ ግብሮች እያከበረ ይገኛል።

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የጥቁር ህዝቦች ድል ተምሳሌት የሆነችው በህዝቦቿ አንድነት መሆኑን ተናግረዋል።

አሁንም በኢትዮጵያ ድህነትን ለማስወገድ እና ሰላምን ለማፅናት ሌት ተቀን የሚሰራ ህዝብ አለ ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው፣ ይህን የፅናት ተምሳሌት የሆነ ተግባርንም በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይ መድገም ይገባል ብለዋል።

በመድረኩም የፓናል ውይይትን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ መርሃ ግብርሮች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

በራሄል አበበ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review