በቻይና በተካሄደው ማራቶን ውደድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

You are currently viewing በቻይና በተካሄደው ማራቶን ውደድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

AMN ጥቅምት 23/2018 ዓ.ም

በቻይና በቤጂንግ እና ሆንዙ በተካሄደው ማራቶን ውድድር በሁለቱም ፆታዎች ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸንፈዋል።

በሆንዙ የማራቶን ውድድር በሴቶች አትሌት ሩቲ አጋ በ2:24:29 ውድድሩን አሸንፋለች ።

በወንዶች አትሌት ጫሉ ደሶ በ2:11:15 በቀዳሚነት አጠናቋል ።

በቤጂንግ በተካሄደው ማራቶን ውድድር በወንዶች አትሌት ለሚ ብርሃኑ 2:08:10 በመግባት ሲያሸንፍ አትሌት ደሳለኝ ግርማ ሁለተኛ ወጥቷል።

በሴቶች አትሌት አንቻሉ ደሴ በ2:26:06 በቀዳሚነት አጠናቃለች ።

ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ቁፍቱ ጣሂር ሦስት መዉጣቷን ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review