ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ ልታዘጋጅ መሆኑ ተሰምቷል፡፡
ከ2 ዓመት በኋላ እንደ አውሮፓዊያኑ የዘመን ስሌት በ2027 ለሚካሄደው 32ኛው የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ (COP32) ኢትዮጵያ አስተናጋጅ ሆና መመረጧን የዘንድሮው የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ (COP30) ፕሬዝዳንት ማስታወቃቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የCOP30 ተሳታፊ ሀገራት 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ጉባኤ በኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ ለማካሄድ በመርህ ደረጃ መስማማታቸውን ነው ፕሬዝዳንት አንድሬ ኮርያ ዶ ላጎ ያስታወቁት፡፡
ይሁን እንጂ ምርጫው በመደበኛነት ተቀባይነት ሊኖረው ይገባል ያሉት ፕሬዝደንቱ ይሄም ዛሬ ማክሰኞ ይካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅ አብራርተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ከናይጄሪያ ጋር ተወዳድራ ነው የተመረጠችው፡፡
ለቀጣዩ አመት COP31 አስተናጋጅ ሃገር ምርጫ አሁንም አከራካሪ መሆኑን ያነሱት ፕሬዝዳንቱ አውስትራሊያ እና ቱርክ ቀጣዩን ጉባኤ ለማዘጋጀት እየተወዳደሩ መሆኑን አስታውቀዋል።
በካሳሁን አንዱአለም