በፓን አፍሪካ ንቅናቄ ሚናቸው ስመጥር የሆኑ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ቤተሰቦች የታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል።
የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዲኤታ ተስፋሁን ጎበዛይ ለጎብኚዎች ገለጻ አድርገዋል።
ከጎብኚዎቹ የቀድሞ የፓን-አፍሪካ አቀንቃኝ መሪዎች ቤተሰብ አባላት መካከል የኔልሰን ማንዴላ፣ የኩዋሚ ንክሩማ፣ የጁሊየስ ኔሬሬ፣ ኮለኔል ሙዓመር ጋዳፊ ቤተሰብ አባላት ይገኙበታል።