ሀያት ረመዳን የአዲስ ታለንት ሾው አሸናፊ በመሆን የ2 ሚሊየን ብር ተሸላሚ ሆነች

You are currently viewing ሀያት ረመዳን የአዲስ ታለንት ሾው አሸናፊ በመሆን የ2 ሚሊየን ብር ተሸላሚ ሆነች

AMN-ታኅሣሥ 29/2018

ለአንድ ዓመት የዘለቀው የአዲስ ታለንት ሾው ዛሬ በአድዋ ድል መታሰቢያ ፍጻሜዉን አግኝቷል።

በአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ በልዩነት የመጣው “አዲስ ታለንት” ሾው በሰባት ምዕራፎች ሲካሄድ ቆይቷል።

ሃያት ረመዳን በድምፅ ውድድር የአዲስ ታለንት ሾው አሸናፊ ሆናለች።

ለሽልማቱ የተዘጋጀውን 2 ሚሊየን ብር የተሸለመች ሲሆን በተጨማሪም የስኬት ባንክ ያዘጋጀውን ስኬት አዋርድ ዋንጫንም ማግኘት ችላለች።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review