AMN – የካቲት 8/2017 ዓ.ም
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንት አኪንውሚ አደሲና እና ከዓለም የእርሻ ልማት ፈንድ ፕሬዝዳንት አልቫሮ ላሪዮ ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ግብርና ዘርፍ እያደረጉት ባለው ድጋፍ ዙሪያ ከሁለቱ ተቋማት ፕሬዝዳንቶች ጋር መወያየታቸውን በኤክስ ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት አመልክተዋል፡፡