ከሸማችነት ወደ አምራችነት – በ”አዲስ አበባ ታምርት”

You are currently viewing ከሸማችነት ወደ አምራችነት – በ”አዲስ አበባ ታምርት”

– በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው የ”ኢትዮጵያ ታምርት” አካል የሆነው “አዲስ አበባ ታምርት” ንቅናቄ በከተማዋ ኢኮኖሚ ላይ አዲስ ተስፋና ተጨባጭ ለውጥ እያስመዘገበ ይገኛል።

– ንቅናቄው የከተማዋን የኢኮኖሚ መዋቅር በመቀየር ረገድ የላቀ ሚና እየተጫወተ ነው።

– ከዚህ በፊት በግብዓትና በኤሌክትሪክ እጥረት ከአቅም በታች ያመርቱ የነበሩ ፋብሪካዎች፣ አሁን ላይ የማምረት አቅማቸውን በከፍተኛ ሁኔታ አሳድገዋል።

– በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ “የኢትዮጵያን ምርት ይግዙ” የሚለው ጥሪ ዛሬ በተጨባጭ ውጤት ታጅቦ በምግብና መጠጥ፣ በጨርቃጨርቅና በኮንስትራክሽን ዘርፎች ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ጥራት ባላቸው ምርቶች መተካት ተችሏል።

– ንቅናቄው በሺዎች ለሚቆጠሩ ወጣቶችና ሴቶች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድል ከመፍጠሩም ባለፈ፣ የቴክኖሎጂና የክሕሎት ሽግግር እንዲመጣ አድርጓል።

– በርካታ አነስተኛ አምራቾች ወደ መካከለኛ ኢንዱስትሪነት ተሸጋግረዋል፤ ጠንካራ የገበያ ትስስርም ተፈጥሮላቸዋል።

– ከጫማ እስከ አልባሳት፣ ከቤት ዕቃዎች እስከታሸጉ ምግቦች ድረስ አዲስ አበባ ከውጭ የምታስገባቸውን ምርቶች በሀገር ውስጥ መተካት አስችሏታል።

– የከተማ አስተዳደሩ ለዘርፉ ስኬት ቁልፍ የሆኑ ድጋፎችን እያከናወነ ይገኛል።

– በከተማዋ በተለያዩ ክፍለ ከተሞች የተገነቡ ሼዶች ለወጣቶችና ለባለሀብቶች ተላልፈው፣ አዲስ አበባን የኢንዱስትሪ ማዕከል እያደረጓት ይገኛሉ።

– ዘመናዊ የኢንዱስትሪ መንደሮችን በማስፋፋት ለአምራቾች ምቹ የሥራ ቦታ እንዲሆኑ ማድረግ ተችሏል።

– ለኢንተርፕራይዞች የማሽነሪ ግዢ የሚውል የሊዝ ፋይናንስና የብድር አገልግሎት እንዲመቻችና የቢሮክራሲ ማነቆዎችን የሚፈታ “የአንድ ማዕከል” አገልግሎት እንዲቋቋም ተደርጓል።

– የባንክ በሮች ለአምራቾች ክፍት ሆነዋል። ንቅናቄው አምራቾች በቀላሉ የሥራ ማስኬጃ ብድር የሚያገኙበትን መንገድ ከማመቻቸቱም በላይ፣ በቀጥታ ከሸማቹ ጋር የሚገናኙባቸውን ታላላቅ ባዛሮች በማዘጋጀት የገበያ ሰንሰለቱን አሳጥሮታል።

– በተጨማሪም አምራቾች ምርቶቻቸውን እንዲያስተዋውቁ ትላልቅ ባዛሮችንና ኤግዚቢሽኖችን በማዘጋጀት በኩልም ከፍተኛ አስተዋጽዖ እያደረገ ይገኛል።

በአስማረ መኮንን

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review