በሕንድ ሃይድራባድ በተዘጋጀው የ’ሚስ ወርልድ ዓለም አቀፍ የቁንጅና ውድድር ላይ ኢትዮጵያን ወክላ የተሳተፈችዉና 2ኛ የወጣችው ሞዴል ሀሴት ደረጄ የመንግስት ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ደማቅ አቀባበል ተደርጎላታል፡፡
የባህል እና ስፓርት ሚኒስትር ዴኤታ ረ/ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ፣ የባህል እና ስፓርት ሚኒስትር ዴኤታ ነፊሳ አልማሀዲ፣ የአዳስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሂሩት ካሳ (ዶ/ር) በዓለም አቀፍ ደረጃ 2ኛ ከአፍሪካ ቀዳሚውን ስፍራ ይዛ ላጠናቀቀቸዉ ሃሴት ደረጄ አቀባበል አድርገዋል፡፡