የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የሁለተኛ ዙር ሰልጣኞች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየጎበኙ ነው፡፡

የጉብኝቱ ተሳታፊ አመራሮች እንደገለጹት፣ በአዲስ አበባ የተሰሩ የልማት ስራዎች ዘርፈ ብዙ ከመሆናቸዉም ባሻገር ልምድ የሚቀሰምባቸዉ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

በጉብኝት መርሀ-ግብሩም በጤና ቱሪዝም፣ በገበያ ማረጋጋት፣ በተቋማት ግንባታ የተከናወኑ ተግባራት፣ በመዲናዋ የተሰሩ የቤት አቅርቦት ስራዎች፣ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክቶች እና ሌሎችም የልማት ስራዎች ይጎበኛሉ።
በትባረክ ኢሳያስ