የአከባቢ ጥበቃ ስርአታችን ደካማ በመሆኑ በድጋሚ ለመተካት እጅግ አስቸጋሪና ለም የሆነውን አፈራችንን ስናጣ ቆይተናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር)።
በህዝብና በመንግስት ትብብር የተጀመረው የአከባቢ ጥበቃ ሥራ የዝናብ ወራት ከመቃረቡ በፊት መሰራት መጀመሩ ተስፋ ሰጪ ነው ብለዋል።
የተፈጥሮ ሃብቶቻችንን በሁሉም መልክ ማልማት የሰርክ ተግባራችን ይሁን። እንበርታ፣ እጆቻችን አፈር ይንኩ፣ ሀገር እናልማ! ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው መልእከታቸውን አጋርተዋል ።