AMN ሐምሌ 7/2018

ባለፉት አምስት ዓመታት ከ200 ሺህ በላይ የሠላም ሠራዊት አባላት ተደራጅተዋል፤
ከ10 ሺህ በላይ የህዝብ ቅጥር ጥበቃ በማደራጀት፣ በማሰልጠንና በማሰማራት ህዝባዊ ሚናቸውን እንዲወጡ ተደርጓል፤

የጸጥታ መዋቅሩ፣ የሰላም ሰራዊት አደረጃጀቱ እና ነዋሪው በቅንጅት በመስራት ላይ ይገኛሉ፤
በየጊዜው የሚነሱ የጸረ ሰላም ኃይሎችን ትንኮሳ ማምከን ተችሏል፤
አስተማማኝ እና ዘላቂነት ያለው ስራ በመሰራቱ መዲናዋ “ የሰላም ከተማ ” በመባል በምሳሌነት ተጠቃሽ ሆናለች፤

ደንብ መተላለፎችን የመከላከልና የመቆጣጠር ስራዎች ተጠናክረዉ ቀጥለዋል፤
በከተማዋ የሚታዩ ህገ-ወጥ ድርጊቶችን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነስ ተችሏል፤
ህገ-ወጥ የመሬት ወረራ፤ ህገ-ወጥ ማስታወቂያ ፣ ህገ-ወጥ የጎዳና ንግድ፣ ህገ-ወጥ እንስሳት ዝውውርና እርድን መቀነስ ተችሏል

ህገ-ወጥ የመንገድ አጠቃቀም፤ ህገ-ወጥ የግንባታ የቁጥጥር ስራዎችን ጨምሮ የተለያዩ የደንብ መተላለፎችን በዘላቂነት መቀነስ ተችሏል
የነዋሪውን ንብረትና መብት ማስከበር ላይ መሰረታዊ ለውጥ ተመዝግቧል

ሰላምን የማወክና ግጭት የማስነሳት እኩይ እቅዶችና ፍላጐቶች ቢያጋጥሙም መዲናዋ ፍፁም ሰላማዊ ሆናለች፤
የከተማዋን ሰላም አስተማማኝ ማድረግ ተችሏል
የህግ የበላይነትን ማረጋገጥ ተችሏል
የከባድ ወንጀል ምጣኔ ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ 47% በላይ እንዲቀንስ ማድረግ ተችሏል።