የማንሠራራት ቀን ዘላቂ ልማት ለሀገራዊ ማንሠራራት
ኢትዮጵያ ተነሥታለች፡፡ ከእንግዲህ ወደኋላ አትመለስም፡፡ ይሄ የማንሠራራት ጉዞዋ በዘላቂ ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የታገዘ መሆን አለበት፡፡
በተለይም በማዕድን፣ በቱሪዝም፣ በግብርና፣ በአምራችነት እና በአይሲቲ ዘርፎች የላቁ ውጤቶችን እያስመዘገብን መቀጠል አለብን፡፡

ለዕድገታችን አጋዥ የሚሆን ሀብት መፍጠር እና ገቢ መሰብሰብ ይገባናል፡፡ ዕድገታችን የሚያመነጨውን ገቢና ሀብትም በሚገባ ሰብስበንና ቆጥበን ለብልጽግና ግባችን መጠቀም አለብን፡፡
የጀመርነውን የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም በማሣለጥና በማሳካት የኢትዮጵያ ማንሠራራት ወደ ዘላቂ የኢትዮጵያ ብልጽግና እንዲለወጥ እናደርጋለን፡፡