AMN – ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም
ኪነ-ጥበብ ወጣቶች ሀገር ወዳድ እንዲሆኑ፣ ሀገራቸውን እንዲያለሙ እና ስለሀገራቸው ጠንካራ የወል ትርክት እንዲኖራቸው ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ።
የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ “ጽኑ ሀገር በኪነ-ጥበብ” በሚል መሪ ሀሳብ አብርሆት የጥበብ ማዕድ መድረክ በቀበና ፓርክ አካሂዷል።
በመድረኩ ላይ ወጣት እና ታዋቂ የኪነ-ጥበብ ባለሙያዎችን ጨምሮ በየክፍለ ከተማው የሚገኙ የኪነ-ጥበብ ማዕከላት የተለያዩ ኪናዊ ሥራዎቻቸውን ለተመልካች አቅርበዋል።
የአዲስ አበባ ባህል እና ኪነ-ጥበብ ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሉባባ ጀማል በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ ቢሮው በየጊዜው መሰል የኪነ-ጥበብ መድረኮችን ማዘጋጀቱ ሕዝብን ከሕዝብ የሚያገናኝ የአብሮነት ድልድይ ፈጥሯል።
መድረኩ ወጣቶች የፈጠራ ችሎታቸውን እንዲያዳብሩ እና በመዲናዋ የተከናወኑ ታላላቅ የልማት ሥራዎችን እንዲያውቁ ሰፊ ዕድል የፈጠረ መሆኑ ተመላክቷል።
በደሳለኝ ሙሐመድ