AMN- ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአፍሪካ ዋንጫ ማጣርያ የምድብ 10 የመጀመርያ ጨዋታ የሱዳን አቻውን በደቡብ ሱዳን ጁባ ከተማ ይገጥማል።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን እንደገለፀው ፣የሱዳን እግር ኳስ ማኅበር የሜዳውን ጨዋታ ለማድረግ የደቡብ ሱዳኑን ጁባ ናሽናል ስታዲየም መምረጡን አሳውቋል።
በወጣው መርሃ ግብር መሠረት ጨዋታው ዓርብ መስከረም 15 ቀን 2019 ዓ/ም ምሽት 1:00 ላይ እንደሚካሄድ ፌደሬሽኑ ገልጿል።