AMN-የካቲት 21/2017 ዓ.ም
በአዲስ ከተማ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7 ሀብተጊዮርጊስ ድልድይ አካባቢ በመኖሪያ እና ንግድ ቤቶች ላይ የእሳት አደጋ ደርሷል።
አደጋው ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 10:35 ሰዓት መከሰቱ ተነግሯል።

የደረሰዉን የእሳት አደጋ ለመቆጣጠር ሰፊ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ እሳት እና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ የሆኑት አቶ ንጋቱ ማሞ ለኤ ኤም ኤን ዲጂታል ተናግረዋል።
ኤ ኤም ኤን ስለ አደጋው እየተከታተለ ዝርዝር መረጃ ወደ እናንተ ያደርሳል