ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም ቁንጅና ዉድድር አሸናፊ ለሆነችዉ ሀሴት ደረጀ ሽልማት አበረከቱ

You are currently viewing ከንቲባ አዳነች አቤቤ በዓለም ቁንጅና ዉድድር አሸናፊ ለሆነችዉ ሀሴት ደረጀ ሽልማት አበረከቱ

AMN ግንቦት 30/2017

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ72ኛው የዓለም ቁንጅና ውድድር ላይ በማሸነፍ የኢትዮጵያ ስም በዓለም መድረክ ከፍ ብሎ እንዲጠራ ላደረገችው የዓለም ቁንጅና አሸናፊ (Miss World) ሀሴት ደረጀ ሽልማት አበርክተዋል፡፡

ከንቲባዋ ይህንን ሽልማት ያበረከቱት “ሀገር እና ጥበብ ለኢትዮጵያ ማንሰራራት” በሚል መሪ ሀሳብ በተዘጋጀው ከተማ አቀፍ የኪነጥበብ ባለሞያዎች ውይይት መድረክ ላይ ስሆን፣ ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ በዓለም መድረክ ላይ አሸናፊ መሆን እንደምትችል የሀሴት ደረጀ ድል ምስክር ነው ብለዋል።

ሀሴት ዉጫዊ ብቻ ሳይሆን በርካታ ዉስጣዊ ቁንጅና እና ብቃት ስላሳየችን ለብዙ ወጣቶች እና ልጆች የእንችላለን ምሳሌት ነች ብለዋል።

በመድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ቱሪዝም እና ባህል አምባደር ሆና እድትሰራ ተልእኮ ሰጥተዋታል።

የዓለም ቁንጅና አሸናፊ (Miss World) ሀሴት ደረጀም ለተደረገላት ሽልማት እና ተልእኮ ማመስገኗን ከከንቲባ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል፡፡

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review