AMN ጥር 20/2018 ዓ.ም
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከአሜሪካው ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ክሪስቶፈር ላንዳው ጋር በጽ/ቤታቸዉ ተወያይተዋል።
ሁለቱ ወገኖች በኢትዮጵያ እና በአሜሪካ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የበለጠ ማጠናከር በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ መክረዋል።
በተጨማሪም የጋራ ፍላጎት ባላቸው ቀጣዊ ጉዳዮች ላይ ሃሳብ ተለዋውጠዋል።
ኢትዮጵያ እና አሜሪካ የ120 ዓመታት የዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ታሪክ እንዳላቸዉ ከዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነዉ መረጃ ያመላክታል፡፡