የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር ከሌሎች ዉድድሮች በምን ይለያል?

You are currently viewing የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር ከሌሎች ዉድድሮች በምን ይለያል?

AMN – ሚያዝያ 9/2018 ዓ.ም

የዓለም አትሌቲክስ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድሮች በአትሌቲክስ ዓለም ውስጥ እጅግ ማራኪ እና ከፍተኛ ተከታታይ ካላቸዉ ዉድድሮች አንዱ ነዉ፡፡

እነዚህ ውድድሮች እንደ ኦሊምፒክ ወይም የዓለም ሻምፒዮና ለሳምንታት የሚቆዩ ሳይሆኑ፣ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ተጀምረው የሚጠናቀቁ ደመቅ ያሉ ሁነቶች ናቸው።

ይህ በዓለም አትሌቲክስ ስር የሚገኝ ከፍተኛውና ዝነኛው የአንድ ቀን ውድድር ተከታታይ ሲሆን በየዓመቱ እንደ ዶሃ፣ ፓሪስ፣ ኦስሎ፣ ዙሪክ እና ሌሎች የዓለም ከተሞች ይዘጋጃል፡፡

በዉድድሩ የሚሳተፉ አትሌቶች በየዙሩ ነጥብ ይሰበስባሉ፤ በመጨረሻም የሊጉን ዋንጫ እና ከፍተኛ የገንዘብ ሽልማት ያገኛሉ።

ይህ የአንድ ቀን የሩጫ ውድድር ላይ በዓለም የታወቁ ምርጥ አትሌቶች ብቻ የሚሳተፉበት መድረክ ነው።

ዉድድሩ ከዳይመንድ ሊግ ቀጥሎ ያለ የውድድር ደረጃ ሲሆን፣ አላማዉም ለበርካታ አትሌቶች የውድድር ዕድል ለመስጠት እና አትሌቲክስን በሁሉም አህጉራት ለማስፋፋት የታለመ ነው።

ውድድሮቹ አብዛኛውን ጊዜ ከ2 እስከ 3 ሰዓታት ባለው ጊዜ ውስጥ የሚጠናቀቁ ሲሆኑ በዝላይ፣ ውርወራ እና ከአጭር እስከ ረጅም ርቀት በተመረጡ ጥቂት ውድድሮች ላይ ብቻ ትኩረቱን ያደርጋል፡፡

አትሌቶች በእነዚህ ውድድሮች ላይ በሚያስመዘግቡት ውጤት መሠረት ለኦሊምፒክ ወይም ለዓለም ሻምፒዮና ለማለፍ የሚረዳቸውን ዓለም አቀፍ ደረጃ ያሻሽላሉ።

የኢትዮጵያ አትሌቶች በተለይም በመካከለኛና በረጅም ርቀቶች ላይ ገናና ስም ያላቸዉ ሲሆኑ ብዙ የዓለም ክብረ ወሰኖች የሚሰበሩት በእነዚህ የዳይመንድ ሊግ ውድድሮች ላይ ነው።

እነዚህ ውድድሮች አትሌቶች ብቃታቸውን የሚፈትሹበት፣ ገቢ የሚያገኙበት እና ስማቸውን የሚያስጠሩበት ዓመታዊ የውድድር መድረኮች መሆናቸዉ የአለም አትሌቲክስ መረጃ ያመላክታል፡፡

አዲስ አበባ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም ግራንድ ፕሪክስ የአንድ ቀን ፉክክርን ለመጀመሪያ ጊዜ የምታስተናግድ ሲሆን በዚህ ዓለም አቀፍ ውድድር ላይ ስመ ጥር አትሌቶች ይሳተፋሉ፡፡

በወንድማገኝ አሰፋ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review