AMN – የካቲት 21/2017 ዓ.ም
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በድምቀት እንዲከበር ላበረከተው አስተዋጽኦ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ዕውቅና ተበርክቶለታል፡፡
19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በእውቅና እና የማጠቃለያ መድረክ ላይ የላቀ አስተዋጽዖ ላበረከቱ ክልሎችና የከተማ አስተዳደሮች እውቅና ሲሰጥ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ልዩ ተሸላሚ ሆኗል።
ልዩ ሽልማቱንም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልከድር ተቀብለዋል።
በታሪኩ ለገሰ