በቴክሳስ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 81 ሲደርስ በርካቶች የደረሱበት አልታወቀም

You are currently viewing በቴክሳስ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የሟቾች ቁጥር 81 ሲደርስ በርካቶች የደረሱበት አልታወቀም

AMN – ሰኔ 30/2017 ዓ.ም

በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት አርብ እለት የተከሰተውን የጎርፍ አደጋ ተከትሎ የሟቾች ቁጥር በትንሹ 81 የደረሰ ሲሆን ሌሎች 41 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም።

የአደጋው ሰለባዎች ቁጥር በፍጥነት እየጨመረ ሲሆን የሟቾች ቁጥር አሁንም ሊጨምር እንደሚችል ባለስልጣናትን ጠቅሶ ቢቢሲ ዘግቧል።

እየቀጠለ ያለው ከባድ የአየር ሁኔታ ለነፍስ አድን ስራው እንቅፋት እንዳይሆን ስጋት አስከትሏል።

በሊያት ካሳሁን

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review