AMN – ሰኔ 9/2018 ዓ.ም
እንደ ሀገር 8 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል የጀመርነው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራም ታሪካዊ ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለጹ፡፡
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላፉት መልዕክት ፣ ትላንት በቢሾፍቱ የነበረን ቆይታ እጅግ አስደማሚ ነበር ብለዋል።
በአፍሪካ ትልቁ የአቪየሽን ፕሮጀክት የሆነው የቢሾፍቱ የአየር ማረፊያ ግንባታ እጅግ አስደማሚ ነው ሲሉ ገልጸዋል።

ከንቲባዋ በመልዕክታቸው “ተስፋን እንትከል“ በሚል ያካሄድነው እንደ ሀገር 8 ቢሊዮን ችግኝ ለመትከል የጀመርነው የአረንጓዴ አሻራ ፕሮግራምም ታሪካዊ ነው ብለዋል።