አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኔዘርላንድ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

You are currently viewing አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኔዘርላንድ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኔዘርላንድ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ጋር ተወያዩ

AMN – ጥር 13/2017 ዓ.ም

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከኔዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ስቲጅን ጃንሰን ጋር በጽ/ቤታቸው ውይይት አድርገዋል።

ውይይቱ በሁለትዮሽ ትብብር፣በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና ፀጥታ ጉዳዮች ያተኮረ እንደነበር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

አምባሳደር ምስጋኑ የኔዘርላንድ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ የኢንቨስትመንት እያደረጉት ያለው ተሳትፎ ተምሳሌታዊ ፋይዳ ገልጸው ፥ በመተግበር ላይ ባለው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የተፈጠሩ ዕድሎችን በስፋት እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል ።

የኔዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ስቲጅን ጃንሰን ኢትዮጵያ ቀጣናውን ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የምታደርገውን ጥረት አድንቀው ኔዘርላንድስ ያላትን ድጋፍ ገልጸዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review