ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና የፓርቲዉ ፕሬዚዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በሰጡት ማጠቃለያ እና የስራ መመሪያ ዛሬ መጠናቀቁን ገለጹ

You are currently viewing ከንቲባ አዳነች አቤቤ ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና የፓርቲዉ ፕሬዚዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በሰጡት ማጠቃለያ እና የስራ መመሪያ ዛሬ መጠናቀቁን ገለጹ

AMN ጥቅምት 30/2018

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባሰፈሩት መልዕክት “በመደመር መንግሥት ዕይታ፣ የዘርፎች እመርታ” በሚል መሪ ሀሳብ ለተከታታይ 11 ቀናት ለብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና የፓርቲያችን ፕሬዚዳንት እና ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በሰጡት ማጠቃለያ እና የስራ መመሪያ ዛሬ ተጠናቅቋል ብለዋል።

የፓርቲያችን ፕሬዝዳንት የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብልፅግና በአጭር ጊዜ ለማረጋገጥ ፣ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ የልማት ስራዎችን ይበልጡን ለማስፋት እና ለማላቅ ፣ የሕዝባችንን ሁለንተናዊ የመልማት ጥያቄዎችን ለመመለስ ስራዎችን በፈጠራ እና ፍጥነት መርህ በማብዛት መከወን እንደሚገባ አንስተዋል ።

እንዲሁም በቀጣይ የአመራሩን ትኩረት የሚሹ ግቦችን ጭምር በየፈርጁ በመለየት አቅጣጫ የተቀመጡ ሲሆን አመራሩም በከፍተኛ መነሳሳት ለመፀም ቃል ገብቷል ።

ይህ በአዳማ ከተማ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ሲሰጥ የነበረዉ ስልጠና ከትላንት በስተያ በኦሮምያ እንዲሁም በትላንትናዉ እለት በአዲስ አበባ በፓርቲያችን እሳቤ የተከናወኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በመጎብኘት እና ልምድ የመለዋወጥ መርሃ ግብር ጭምር የተካሄደ ነበር ብለዋል።

በመስክ ጉብኝታችን ያገኘናቸው በርካታ ስኬቶች በምናብ ከፍታ፣ በአመራር ትጋትና በህዝባችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ የኢትዮጵያ ብልጽግና አይቀሬነት ማሳያ መሰረቶች ናቸዉ።

የተገኙ ዉጤቶች እንደተጠበቁ ሆነዉ ገና አዳዲስ ነገሮችን እንፈጥራለን! እንፈጥናለን! የኢትዮጵያ ብልጽግና እናረጋግጣለን ሲሉ ገልጸዋል።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review