ሰላም የሰፈነባትና የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት ከተማ መፍጠር ተችሏል

You are currently viewing ሰላም የሰፈነባትና የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት ከተማ መፍጠር ተችሏል

AMN AMN- ጥር 02/2018 ዓ.ም

የከተማዋ ነዋሪዎችና እንግዶቿ በሰላም ወጥተው የሚገቡበት እና የሕግ የበላይነት የተረጋገጠባት ከተማ መፍጠር ተችሏል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ተናገሩ።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ እና ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ እያካሄዱ ነው ።

በመድረኩ የየተቋማቱ ከማዕከል እስከ ወረዳ የሚገኙ አመራሮች ተሳትፈዋል::

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ በዚህ ወቅት እንዳሉት ህብረተሰቡን በማሳተፍ እና በቴክኖሎጅ የተደገፈ ስራ በመሰራቱ የከተማዋ ነዋሪዎችና እንግዶቿ በሰላም ወጥተው የሚገቡባት ከተማን መፈጠር ተችሏል ብለዋል::

ባለፉት 6 ወራት ሃሰተኛ ሰነድ የሚያዘጋጁ ግለሰቦችን ጨምሮ ሕግ ወጥ መሳሪያ እና ገንዝብ አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል እንደተቻለም ተናግረዋል::

ሀገር አቀፍ እና ዓለም አቀፍ ሁነቶች በስኬት እንዲጠናቀቁ ማድረግ ሌላዉ በ6 ወሩ የተከናወነ ተግባር መሆኑንም ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ገልጸዋል፡፡

ባለፉት 6 ወራት 33 ሺህ የሰላም ሰራዎት አባላት ስልጠና ወስደው ወደ ስራ መግባታቸዉንም ኃላፊዋ ተናግረዋል::

ህገ ወጥ የመሬት ወረራን፣ ህገ ወጥ ግንባታ እና የጎዳና ላይ ንግድን ከመከላከል አኳያም ተጨባጭ ዉጤቶች ተገኝተዋል ተብሏል::

በቴዎድሮስ ይሳ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review