AMN ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ/ም

የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን አስመልክቶ የእስልምና እምነት ተከታዮች በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሶላት ስነ- ስርዓት አካሂደዋል።
የኃይማኖት አባቶች እና የእምነቱ ተከታዮች፣ የውጭ ሀገር ዜጎች የመንግስት የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የተካሄደው የሶላት ፕሮግራም በስኬት መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡
የሶላት ስነ-ስርዓቱ እስከሚጠናቀቅ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳያጋጥም ተብሎ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶቸ መከፈታቸውንም ፖሊስ ገልጿል፡፡
ለፕሮግራሙ ስኬታማነት አስተዋፆኦ ላደረጉ አካላት፣ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ለተወጡ የፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና አባላት ፖሊስ ምስጋናዉን አቅርቧል፡፡