AMN – ግንቦት 28/2018 ዓ.ም
ለካቢኔው በዛሬው በቀረቡ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡
በዚህ መሰረት፡-

1ኛ. የገላን ጉራ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተዳደር ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ተፈፃሚ እንዲሆን አፅድቋል።
2ኛ. የመሬት ይዞታ ማስለቀቅና ካሳ ጉዳዮች ይግባኝ ሰሚ ጉባኤ እንደገና ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ አፅድቋል።
3ኛ. በግል ዘርፍ ለህክምና ተቋማት ግንባታ እና ማስፉፍያ የሚውል መሬት ለማስተላለፍ የቀረበ የዉሳኔ ሀሳብ ላይ ተወያይቶ፣ ተፈፃሚ እንዲሆን አድፅድቋል።