AMN ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም

የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ከወረዳ እስከ ፌዴራል፣ እንዲሁም ዲያስፖራውና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተጀምሯል።
ምክክር እንደ ተለመደው የፖለቲካ ክርክር ወይም በአብላጫ ድምፅ የሚወሰን ሳይሆን፣ በጋራ መግባባት ላይ የሚደረስበት ታሪካዊ ሂደት ነው።
4 ሺህ ተሳታፊዎች ለስምንቱ አጀንዳዎች ዝርዝር ማብራሪያና የውሳኔ አሰጣጥ ስነ-ዘዴዎች ላይ ስልጠና ወስደዋል።
ሂደቱ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች፣ ክልሎች ሳይቀሩ እኩል ድምፅና መስተጋብር እንዲኖራቸው ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ነው።
በሂደቱ መሳተፍ የሚፈልጉ ተጨማሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ታጣቂዎች አሁንም በሩ ክፍት መሆኑን ኮሚሽነሩ ገልጸዋል።
ቅዳሜና እሁድ የነበሩ ጥቃቅን የአደረጃጀት ክፍተቶች ተስተካክለው፣ ከሰኞ ጀምሮ ሙሉ አቅም ያለው የቡድን ውይይቶች ይጀምራሉ።
የሚዲያ አካላት ሂደቱን በየክልሉ በሚነገሩ ቋንቋዎች ለህዝቡ በማድረስ ረገድ ያላቸው ሚና ከፍተኛ መሆኑን አሳስበዋል።