“ዘላቂ እና ሕዝብን ማዕከል ያደረገ አረንጓዴ ሽግግር” በሚል ጭብጥ እየተካሄደ ባለው የ2025 ፒ4ጂ ቬይትናም ጉባኤ የአየር ንብረት ጥበቃን ለማራመድ አስፈላጊ የሆኑ ሶስት ቁልፍ የተግባር ነጥቦችን አፅንዖት ሰጥቼ አንስቻለሁ – ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የቬይትናም ጠቅላይ ሚኒስተር ክቡር ፋም ሚን ቺን በይፋዊ ጉብኝታችን ወቅት ላደረጉልን የደመቀ አቀባበል እና የክብር መስተንግዶ አመሰግናለሁ። ኢትዮጵያና ቬይትናም የሚያመሳስሏቸው ብዙ የጋራ ጉዳዮች አሏቸው። ሁለታችንም ትልቅ እና ለሥራ የተነሳሳ ወጣት ሕዝብ ያለን፣ ለልማት እና እድገት የቆረጠ‍ን እንዲሁም በታሪካችን ሂደትም በፅናታችን የምንታወቅ ሀገራት ነን።