በቱሪዝም ዘርፍ
አዲስ አበባ ባለፉት ስድስት ወራት 150 የሚሆኑ ዓለም አቀፍና አሕጉር አቀፍ ኩነቶች አስተናግዳለች ።
4 ነጥብ 9 ሚሊየን የሀገር ውስጥ ቱሪስቶች መዲናዋን ጎብኝተዋል።
699 ሺህ 761 የውጭ ቱሪስቶች ከተማዋን ለመጎብኘት የቻሉ ሲሆን ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም የ15 በመቶ ብልጫ አሳይቷል።
ከሀገር ውስጥ እና ከውጪ ሀገር የቱሪስት ፍሰት 155 ቢሊየን ብር ወደ ኢኮኖሚው ፈሰስ ተደርጓል።
የቤት ልማት አቅርቦት
97 ሺህ ቤቶች ባለፉት 6 ወራት በግንባታ ላይ ይገኛሉ።
በመንግስት በጀት እና በበጎ አድራጎት ከ12 ሺህ 257 በላይ የመኖሪያ እና የንግድ ቤቶችን ለልማት ተነሺዎች፣ ለሀገር ባለውለታዎች፣ በጨረታና በመልካም አስተዳደር ተላልፏል።
ባለፉት 6 ወራት ውስጥ በበጎ ፍቃድ አገልግሎት 4 ሺህ 990 ቤቶች ተገንብተዋል።
በመንግስትና የግል አጋርነት እና በከተማው በጀት ሊገነቡ ከታቀዱ 100 ሺህ ቤቶች ላይ 97 ሺህ ቤቶች ባለፉት 6 ወራት ወደ ግንባታ ገብተዋል።
በግል እና ሪል ስቴት የሚገነቡ ቤቶች ክንውን 13 ሺህ 517 ደርሷል።
በኮሪደር የለሙ 810 የንግድ ቤቶች በልማት ለተነሱ አነስተኛ ነጋዴዎች ለማስተላለፍ እየተሰራ ነው።
ከለውጡ በፊት ለጋራ መኖሪያ ቤቶች መገንቢያ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተወሰደው የቦንድ ብድር ከወለዱ ብር 61 ነጥብ 2 ቢሊየን ከለውጡ ወዲህ ተከፍሏል።
ከ70 በላይ የመንግስትና የግል አጋርነት ፕሮጀክቶች ወደ ሥራ ማስገባት የተቻለ ሲሆን፣ ከብር 1 ነጥብ 3 ትሪሊዮን በላይ ካፒታል ኢንቨስትመንት መሳብ ተችሏል።
በአጠቃላይ ባለፉት ስድስት ወራት በከተማ አስተዳደር በተከናወኑ ሥራዎች በአማካይ 95.3 በመቶ አፈጻጸም ተመዝግቧል።
በትዝታ መንግስቱ