አትሌት ታደሰ ታከለ የቶኪዮ ማራቶን አሸነፈ

You are currently viewing አትሌት ታደሰ ታከለ የቶኪዮ ማራቶን አሸነፈ

AMN- የካቲት 22/2018 ዓ.ም

በዓለም አትሌቲከስ የፕላቲኒየም ደረጃ በተሰጠው 19ኛው የቶኪዮ ማራቶን አትሌት ታደሰ ታከለ አሸነፈ ።

አትሌት ታደሰ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2: 03.37 ወስዶበታል፡፡

አትሌቱ ያሳለፍነው ዓመት የቶኪዮ ማራቶንን ማሸነፉ የሚታወስ ሲሆን፣ዘንድሮም ለተከታታይ ጊዜ ማሸነፍ ችሏል።

በውድድሩ የተሳተፉት ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አትሌት ሙክታር እድሪስ በ2:04.07 የግል ምርጥ ስዓቱን በማስመዝገብ በመግባት 5ኛ፣ለሁለተኛ ጊዜ ማራቶን ውድድሩን ያካሄደው

አትሌት ሰለሞን ባረጋ በ2:05.00 በመግባት የግል ምርጥ ስዓቱን በማስመዝገብ

7ኛ ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።

በሴቶች ምድብ አትሌት ብርቱኳን ወልዴ ሁለተኛ ደረጃ ወጥታለች ።

አትሌት ብርቱኳን ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2:16.36 በመግባት የግል ምርጥ ስዓቷን አስመዝግባለች ።

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አትሌት ሀዊ ፈይሳ በ2:17.39 በመግባት ሶስተኛ

፣አትሌት ሱቱሜ አሰፋ በ2:17.39 በመግባት አራተኛ

አትሌት መገርቱ አለሙ በ2:18.50 በመግባት አምስተኛ ደረጃ በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቀዋል ።

አትሌት ሱቱሜ አሰፋ ያለፉት ሁለት ተከታታይ ዓመታት ቶኪዮ ማራቶን ማሸነፏ የሚታወስ ነው።

ኬንያዊቷ አትሌት ብሪጅ ኮስጊ ውድድሩ በ2:14.29 በመግባት አሸንፋለች ።

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review