AMN ሐምሌ 19/2018

የኢኳቶሪያል ጊኒ ሲሞን ኦዮና እሴኖ አንጌ፣ የቦትስዋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ፌንዮ ቡታሌ፣ የኮትዲቫር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናያላ ካባ እና የሩዋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦሊቪዬ ንዱሁንግሬሄ በ49ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ አዲስ አበባ ገብተዋል።

በተጨማሪም የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢብራሂም አል-ባክሪ ኔይ ስብሰባውን ለመካፈል አዲስ አበባ ገብተዋል።

በ49ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ለመሳተፍ የአፍሪካ ሀገራት ልዑካን ቡድን አባላት አዲስ አበባ በመግባት ላይ ይገኛሉ።

በዚሁ መሠረት የኢኳቶሪያል ጊኒ ሲሞን ኦዮና እሴኖ አንጌ፣ የቦትስዋና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ፌንዮ ቡታሌ፣ የኮትዲቫር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናያላ ካባ እና የሩዋንዳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦሊቪዬ ንዱሁንግሬሄ እንዲሁም የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ኢብራሂም አል-ባክሪ ኔይ አዲስ አበባ ገብተዋል።

እንግዶቹ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የፕሮቶኮል ሹም መላኩ በዳዳ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
49ኛው የአፍሪካ ህብረት የስራ አስፈጻሚዎች ስብሰባ ሐምሌ 21 እና 22 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።