በኪነ-ጥበብ ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅም ለመጠቀም በጋራ መስራት አለብን ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለጹ

You are currently viewing በኪነ-ጥበብ ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅም ለመጠቀም በጋራ መስራት አለብን ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ገለጹ

AMN – ታኅሣሥ 6/2018 ዓ.ም

በኪነ-ጥበብ ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅም ለመጠቀም በጋራ መስራት አለብን ሲሉ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ተናገሩ ፡፡

በብሄራዊ ጥቅም የማይደራደር ትውልድ ለመፍጠር የጥበብ ስራዎችን ከፍተኛ አበርክቶ አላቸው ፣ ይህንን ለማሳካት የጥበብ ቤተሰብ ኃላፊነት መወጣት አለበት ብለዋል ሚኒስትሯ ።

የምንፈልገውን አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት የጥበብ ስራዎችን እንጠቀማለን ለዚህም የጥበብ ባለሙያዎች ከፍተኛ ኃላፊነት አለባችሁ ብለዋል ።

የምንፈልገውን አሰባሳቢ ትርክት ለመገንባት እና ሕብረ ብሄራዊ አንድነት ለማጎልበት የጥበብ ስራዎችን እንጠቀማለን ለዚህም በኪነ-ጥበብ ዘርፍ ኢትዮጵያ ያላትን አቅም ለመጠቀም በጋራ መስራት አለብን ነው ያሉት የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ ።

ኪን-ኢትዮጵያ በተለያዩ ዓለም አቀፋ ሀገራት ከሚያደርገው የኢትዮጵያን ባህልና እሴት የማስተዋወቅ ስራ በሀገር ውስጥም ሕዝብ ለሕዝብ ትስስር ለማጠናከር በየክልሎች ይሰራል ብለዋል ።

ባህል በመጠበቅና የኢትዮጵያውያን እሴት በማጎልበት ሂደት ውስጥ የኪነ-ጥበብ ዘርፍ ባለሙያዎች ከፍተኛ ኃላፊነት አለባችሁም ነው ያሉት ፡፡

የኪነ-ጥበብ ፈጠራዎች ስራዎች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም አንጻር ፣ የሥነ-ጥበብ ፈጠራ ስራዎችን ገዥ ትርክትን ከማስረጽ አንጻር ፣ እና የጥበባት እና ፈጠራ ኢንዱስትሪ ፖሊሲ ላይ ከክልል እና ከፌዴራል የተውጣጡ የኪነ – ጥበብ ባለሙያዎች እና የክልል የባህል እና የኪነ-ጥበብ ዘርፍ ኃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል ።

በተጨማሪም ለባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከኪነ-ጥበብ ፣ ከባህል እና ከስፖርት አንጻር በአዋጅ የተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት በተመለከተ በውይይት መድረኩ ገለጻ ተደርጓል ።

በዳንኤል መላኩ

0 Reviews ( 0 out of 0 )

Write a Review