AMN- ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም
ኢትዮጵያውያን ከተወያዩ አንድ ነገር ላይ እንደሚደርሱ አምነን ነበር ያም ተሳክቶልናል ሲሉ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ(ፕ/ር) ገለጹ፡፡
ዋና ኮሚሽነሩ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የመዝጊያ ስነ ስርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር ምክክሩ በስኬት መከናወኑን ተናግረዋል፡፡
ከሀምሌ 8 ጀምሮ በነበረን ቆይታ 4ሺህዎቻችን ተመካክረናል ፣ በሚገባ ተፋቅረናል ብለዋል፡፡
ብዙዎች ይህን ሁሉ ቀናት እንዴት ችለው ተመካክረው ይቆያሉ የሚል ጥያቄ ያላቸው የነበረ ቢሆንም ፣ በምክክሩን በተሳካ ሁኔታ በማካሄድ ኢትዮጵያውያን የመቻል አቅማቸውን አሳይተዋል ብለዋል፡፡
በታደሰ ሽፈራው